​ቅዱስ ጊዮርጊስ ታደለ መንገሻን ሲያስፈርም አሜ መሐመድን ለማስፈረም ተስማምቷል

የፕሪምየር ሊጉ ቻምፒዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ ደደቢትን ለመቀላቀል ተስማምቶ የነበረው ታደለ መንገሻን ባልተጠበቀ ሁኔታ ሲያስፈርም አሜ መሐመድን ለማስፈረም ተስማምቷል፡፡

ያለፉትን ሁለት የውድድር አመታት በአርባምንጭ ያሳለፈው ታደለ መንገሻ ወደ ቀድሞ ክለቡ ደደቢት ለመመለስ ተስማምቶ የነበረ ቢሆንም ባልታወቀ ምክንያት ሳይፈርም ቀርቶ በ2000 እና 2001 የውድድር አመታት ወደተጫወተበት ቅዱስ ጊዮርጊስ ተመልሶ የ2 አመታት ኮንትራት መፈራረሙን የቅዱስ ጊዮርጊስ ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ አስታውቋል፡፡

ሌላው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ፊርማውን ያኖራል ተብሎ የሚጠበቀው አሜ መሐመድ ነው፡፡ አሜ ከጅማ አባ ቡና ጋር የ1 አመት ውል የነበረው በመሆኑ ተጫዋቹ ለጅማ አባ ቡና የውል ማፍረሻ 1,000,000 ብር ለመክፈል ተስማምቶ መልቀቂያ ተቀብሏል፡፡ በቀጣዮቹ ጊዜያትም በይፋ ለክለቡ የሚፈርም ይሆናል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *