​የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ነገ ይጀመራል

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 1ኛ ዲቪዝዮን የ2010 የውድድር ዘመን ነገ በሚደረጉ ጨዋታዎች ይጀመራል፡፡

ውድድሩ ዘንድሮ በአዲስ መልክ የሚካሄድ ሲሆን በ2009 የውድድር አመት በሁለት ምድቦች ተከፍለው ውድድራቸውን ያካሄዱና የመጀመርያዎቹን 5 ደረጃዎች የያዙ 10 ቡድኖች “የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 1ኛ ዲቪዝዮን” የሚል መጠርያ በተሰጠው ሊግ የሚካፈሉ ይሆናል፡፡

የመጀመርያ ሳምንት መርሀ ግብር

ቅዳሜ ህዳር 2 ቀን 2010

09:00 ሲዳማ ቡና ከ መከላከያ

09:00 ደደቢት ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ

09:00 አዳማ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

10:00 ድሬዳዋ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ

እሁድ ህዳር 3 ቀን 2010

09:00 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ጌዲኦ ዲላ


* ነገ እና ከነገ በስቲያ የሚደረጉትን ጨዋታዎች በቀጥታ የውጤት መግለጫ የምናደርሳችሁ ይሆናል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *