ከፍተኛ ሊግ | ሀላባ ከተማ ይቅርታ ጠየቀ

ባሳለፍነው እሁድ በ6ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ሀላባ ከተማ በሜዳው ኢትዮጵያ መድንን ያስተናገደበት ጨዋታ በ76ኛው ደቂቃ ላይ ከተመልካች በተወረወረ ድንጋይ የመሐል ዳኛው ኤፍሬም ደበሌ ላይ ጉዳት በመድረሱ ምክንያት መቋረጡ የሚታወስ ነው። ይህንን አስመልክቶም የሀላባ ከተማ ክለብ ለፌዴሬሽኑ የይቅርታ ደብዳቤ አስገብቷል።

የክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ አንዋር ሲራጅ ስለ ጉዳዩ ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት በተፈጠረው ስርዓት አልበኝነት በጣም እንዳዘኑ ገልፀው የሀላባ ከተማ በእግርኳስ ውድድሮች ባለፉት 10 ዓመታት ሲሳተፍ እንዲህ አይነት ድርጊት ታይቶ እንደማይታወቅ በማውሳት ከጨዋታው መቋረጥ በኋላ አመራሩ እንዲሁም የከተማው አስተዳደር ማምሻውን ስብስባ አድርጎ ወደ እርምጃ በመግባት ሁለት ተጠርጣሪዎችን ወዲያው በመያዝ በቀጣዩ ቀንም 9 ወጣቶችን በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ለፍርድ ለማቅረብ ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል። 

ፕሬዝዳንቱ የሀላባ እግር ኳስ ክለብ እና የከተማው አስተዳደር የተፈጠረውን ሁሉ አጥብቆ እንደሚቃወምና እንዲህ አይነት ድርጊት ዳግም እንዳይፈፀም አጥብቀው እንደሚሰሩ በመግለፅ የሚመለከታቸው አካላትን በክለቡ እና በሀላባ ህዝብና አስተዳደር ስም ይቅርታ መጠየቀቸውን ለሶከር ኢትዮጽያ ገልፀዋል።

ክለቡ ለፌዴሬሽን ያስገባው የይቅርታ ደብዳቤ ይህንን ይመስላል:-

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *