ኢትዮጵያውያን ዳኞች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታ ይመራሉ

ኢትዮጵያውያን ዳኞች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታ ይመራሉ

አራት ኢትዮጵያውያን ዳኞች ወሳኝ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ይመራሉ።

አራት ኢትዮጵያውያን ዳኞች የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታ ይመራሉ። መስከረም 28 ሞሪሽየስ ከ ካሜሩን የሚያካሂዱት የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታ አራት ኢንተርናሽናል ዳኞች ይመሩታል። በቅርቡ የአልጀርያው ቤሎዚዳድ ከ ቡርኪናፋሶው ዶዋንስ በሚሎድ ሀደፊ ስቴድየም ያካሂዱት የካፍ ቶታል ቻምፒዮንስ ሊግ  ጨዋታ በጣምራ የመሩት ኢንተርናሽናል ዳኞች ቴዎድሮስ ምትኩ በዋና ዳኝነት፤ ፋሲካ የኋላሸት ደግሞ በረዳት ዳኝነት እንዲሁም ኢንተርናሽናል ዳኞች አሸብር ታፈሰ በረዳትነት ፤ በላይ ታደሰ ደግሞ በአራተኛ ዳኛነት ጨዋታውን የሚመሩት ሲሆን ጨዋታውም  መስከረም 28 በኮት ዲ ኦር ብሔራዊ የስፖርት ኮምፕሌክስ ውስጥ በሚገኘው ‘National Sports Complex Pitch 1’ ይካሄዳል።