ዛምቢያ 2017: ወደ ጅቡቲ የሚያመሩ 20 ተጫዋቾች ታውቀዋል

የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ከሶማልያ ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ወደ ጅቡቲ የሚያመሩትን 20 ተጫዋቾች ለይቷል፡፡

በመጀመርያው ጨዋታ የማሸነፍያውን ግብ ያስቆጠረው ተስፋዬ ሽብሩ ባጋጠመው ጉዳት ከጉዞው ሲቀር የመከላከያው ሙጃይድ መሃመድ ፣ የጋምቤላ ከተማው ኡጁሉ ኦክሎ የአአ ዩኒቨርሲቲው ያሲን ጀማል ፣ የቡና ተስፋ ቡድኑ ገናናው እንዲሁም የሰበታ ከተማው ተመስገን ገብረኪዳን የተቀነሱ ተጫዋቾች ናቸው፡-

ወደ ጅቡቲ የሚያቀኑት ተጫዋቾች

ግብ ጠባቂዎች

ተክለማርያም ሻንቆ – አዲስ አበባ

በሽር ደሊል – ሙገር ሲሚንቶ

ምንተስኖት የግሌ – ደደቢት

 

ተከላካዮች

ዳግም ንጉሴ – ወላይታ ድቻ

ፈቱዲን ጀማል – ወላይታ ድቻ

ሀይደር ሙስጠፋ – ጅማ አባ ቡና

እንየው ካሳሁን – አዲስ አበባ ከተማ

ደስታ ደሙ – ሙገር ሲሚንቶ

ዳንኤል ራህመቶ – አዲስ አበባ ፖሊስ

ኢብራሂም ሁሴን – ሰበታ ከተማ

 

አማካይ

ኤፍሬም ካሳ – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ሱራፌል ዳኛቸው – አዳማ ከተማ

ዳዊት ተፈራ – ጅማ አባቡና

ክንዳለም ፍቃዱ – ሙገር ሲሚንቶ

ቢንያም በላይ – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ሱራፌል ዳንኤል – ድሬዳዋ ከተማ

ዘሪሁን ብርሃኑ – አአ ከተማ

 

አጥቂዎች

ያሬድ ብርሀኑ – ደደቢት

ኦሜ መሃመድ – ጅማ አባ ቡና

ሱራፌል አወል – ጅማ አባቡና

ብሄራዊ ቡድኑ ከደቂቃዎች በኀላ ወደ ጅቡቲ የሚበር ሲሆን ከሶማልያ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ አርብ ይካሄዳል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *