ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ፡ የደቡብ-ምስራቅ ዞን 2ኛ ዙር ዛሬ ተጀምሯል

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ደቡብ-ምስራቅ ዞን ሁለተኛ ዙር ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች ተጀምሯል፡፡ ጥሩነሽ ዲበባ እና ሲዳማ ቡና ከሜዳቸው ውጪ ድል ሲቀናቸው መሪው ሀዋሳ ከተማም አሸንፏል፡፡

አዳማ ላይ አዳማ ከተማ ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚን አስተናግዶ 2-0 ተሸንፏል፡፡ በጋምቤላ ክልል በታጣቂዎች በተፈፀመው ጥቃት ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች የ1 ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ በተጀመረው ጨዋታ የጥሩነሽ ዲባባን የድል ግቦች ከመረብ ያሳረፉት ናርዶስ ጌትነት እና ዮዲት መኮንን ናቸው፡፡

PicsArt_1461507610447

ወደ አርባምንጭ የተጓቸው ሲዳማ ቡና በአርባምንጭ ላይ የ3-0 ድል ተቀዳጅቷል፡፡ የሲዳማ ቡናን ሶስቱንም ግቦች አስቆጥራ ሐት-ትሪክ የሰራችው አይዳ ኡስማን ነች፡፡

ሀዋሳ ላይ ሀዋሳ ከተማ ድሬዳዋ ከተማን 4-0 በማሸነፍ መሪነቱን አስጠብቋል፡፡ ትብለፅ አፅብሃ ሁለት ግቦች ስታስቆጥር ፅዮን ሳህሉ እና ምርቃት ፈለቀ ቀሪዎቹን የድል ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

 

የደረጃ ሰንጠረዥ

PicsArt_1461508402837

የ7ኛ ሳምንት ጨዋታዎች

ቅዳሜ ሚያዝያ 29 ቀን 2008

09፡00 ሀዋሳ ከተማ ከ አርባምንጭ ከተማ (ሀዋሳ)

09፡00 ድሬዳዋ ከተማ ከ አዳማ ከተማ (ድሬዳዋ)

09፡00 ጥሩነሽ ዲባባ ከ ሲዳማ ቡና (አሰላ)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *