ፕሪሚየር ሊግ ፡ የፍፁም ገብረማርያም ግቦች ኤሌክትሪክን ወደ ድል መልሰውታል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት አንድ ጨዋታ ዛሬ ተደርጎ ኤሌክትሪክ ከተከታታይ ሽንፈቶች ያገገመበትን ድል ደደቢት ላይ አስመዝግቧል፡፡

10:00 ላይ በተጀመረውና በከፍተኛ ዝናብ በታጀበው ጨዋታ ፍጹም ገብረማርያም በ7 እና 72ኛው ደቂቃ የኤሌክትሪክን የማሸነፍያ ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

image

በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ውሃ ያዘለው ሜዳ ኳስን ለማንሸራሸር አዳጋች የነበረ ሲሆን ጨዋታው ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ ቢደረግበትም የግብ እድል በመፍጠር በኩል ጠንካራ የመከላከል አጨዋወት ይዞ የገባው ኤሌክትሪክ የተሻለ ነበር፡፡

የመጀመርያውን ዙር በጥሩ አቋም ያጠናቀቀው ደደቢት በሁለተኛው ዙር ካደረጋቸው 5 ጨዋታዎች ይህ 3ኛ ሽንፈቱ ነው፡፡ በአንፃሩ ኤሌክትሪክ ከ4 ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል በመመለስ በጊዜያዊነት ከወራጅ ቀጠናው ወጥቷል፡፡

የደረጃ ሰንጠረዥ

image

የሊጉ 18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ነገ እና ሰኞ ይቀጥላሉ፡፡

ቅዳሜ ሚያዝያ 29 ቀን 2008
ኤሌክትሪክ 2-0 ደደቢት (አአ ስታድየም)
 
እሁድ ሚያዝያ 30 ቀን 2008

09፡00 አዳማ ከተማ ከ አርባምንጭ ከተማ (አዳማ)
 
09፡00 ወላይታ ድቻ ከ ሲዳማ ቡና (ቦዲቲ)
 
09፡00 ሀዲያ ሆሳዕና ከ ድሬዳዋ ከተማ (ሆሳዕና)
 
10፡00 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ኢትዮጵያ ቡና (አአ ስታድየም)
 
ሰኞ ግንቦት 1 ቀን 2008
 
09፡00 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ሀዋሳ ከተማ (አአ ስታድየም)
 
11፡30 መከላከያ ከ ዳሽን ቢራ (አአ ስታድየም)

የከፍተኛ ግብ አግቢዎች ደረጃ

image

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *