ከፍተኛ ሊግ፡ ጅማ አባ ቡና 1ኛውን ዙር ካለሽንፈት አጠናቋል

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የመጨረሻ ተስተካካይ ጨዋታዎች ዛሬ ተደርገው 1ኛው ዙር ተጠናቋል፡፡ ጅማ አባ ቡና ካለሽንፈት 1ኛውን ዙር ሲያጠናቅቅ ሙገር ወደ ደብረብርሃን ተጉዞ አሸንፏል፡፡

ጅማ አባ ቡና አአ ዩኒቨርሲቲን አስተናግዶ 4-0 አሸንፏል፡፡ የምድብ ለ መሪዎቹን ግቦች አሜ መሃመድ እና ኪዳኔ አሰፋ ሁለት ሁለት ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡ ለኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን የተመረጠው ኪዳኔ በጥሪው ማግስት ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

image

ጅማ አባ ቡና በ1ኛው ዙር ካደረጋቸው 15 ጨዋታዎች 12 በማሸነፍ በሶስት ጨዋታ አቻ በመውጣት ምንም ሽንፈት ሳይቀምስ አንደኛውን ዙር አጠናቋል፡፡

ወደ ደብረብርሃን የተጓዘው ሙገር ሲሚንቶ ሰሜንሸዋ ደብረብርሃንን 1-0 አሸንፏል፡፡ የሙገርን ብቸኛ የድል ግብ ከመረብ ያሳረፈው ኤሪክ ኤልማን ነው፡፡

image

የሁለተኛው ዙር ግንቦት 9 የሚጀመር ሲሆን የ1ኛው ዙር ግምገማ ግንቦት 3 ይደረጋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *