ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ፡ ደደቢት ፣ ንግድ ባንክ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ማጠቃለያ ውድድሩ ማለፋቸውን ከወዲሁ አረጋግጠዋል

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ነው፡፡ለማጠቃለያ ውድድር ማለፋቸውን ያረጋገጡ ቡድኖችም እየታወቁ ነው፡፡

በ10 ክለቦች መካከል የሚካሄደው የማጠቃለያ ውድድር ሰኔ ወር አጋማሽ ላይ በሀዋሳ የሚካሄድ ሲሆን ከመካከለኛ – ሰሜን ዞን 6 ፣ ከደቡብ-ምስራቅ ዞን ደግሞ 4 ቡድኖች ያልፋሉ፡፡
በዚህም መሰረት ደደቢት ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ማለፋቸውን ሲያረጋግጡ መከላከያ ከቀጣይ ጨዋታው 3 ነጥብ ካሳካ ሶስቱን ቡድኖች ይቀላቀላል፡፡ ሀዋሳ ከተማ ከተማ ደግሞ አቻ ውጤት ወደ ማጠቃለያው ለማለፍ በቂው ነው፡፡

የመካከለኛ – ሰሜን ዞን 16ኛ ሳምንት ውጤቶች

እሁድ ሚያዝያ 30 ቀን 2008
ዳሽን ቢራ 4-0 እቴጌ
ማክሰኞ ግንቦት 2 ቀን 2008
ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ 1-1 ኢትዮጵያ ቡና
ረቡዕ ግንቦት 3 ቀን 2008
ልደታ ክ/ከተማ 1-3 ቅዱስ ጊዮርጊስ
መከላከያ 0-0 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ማከሰኞ ግንቦት 9 ቀን 2008
11፡30 ኤሌክትሪክ ከ ሙገር (አአ ስታድየም)

PicsArt_1463053315137

የ17ኛ ሳምንት ፕሮግራም

ቅዳሜ ግንቦት 6 ቀን 2008
09:00 ኤሌትሪክ ከ ኢትዮጵያ ቡና (አአ ስታድየም)
11:00 ሙገር ሲሚንቶ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (አአ ስታድየም)

እሁድ ግንቦት 7 ቀን 2008
09:00 መከላከያ ከ እቴጌ (አአ ስታድየም)
09:00 ዳሽን ቢራ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ (ጎንደር)
11:00 ደደቢት ከ ልደታ (አአ ስታድየም)

የደቡብ-ምስራቅ ዞን 8ኛ ሳምንት ፕሮግራም

እሁድ ግንቦት 9 ቀን 2008
09:00 አርባምንጭ ከተማ ከ ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ (አርባምንጭ)
09:00 ሲዳማ ቡና ከ ድሬዳዋ ከተማ (ይርጋለም)
09:00 አዳማ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ (አዳማ)

የደቡብ-ምስራቅ ዞን 7ኛሳምንት ውጤቶች እና የደረጃ ሰንጠረዥን ይህን ሊንክ ተከትለው ይመልከቱ
soccerethiopia.net/?p=10179
 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *