ከፍተኛ ሊግ ፡ ደቡብ ፖሊስ ያልተጠበቀ ድል ሲያስመዘግብ አክሱም እና ሙገር ነጥብ ተጋርተዋል

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ዛሬ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች አስተናግዶ ደቡብ ፖሊስ ያልተጠበቀ ድል ሲያስመዘግብ አክሱም ከ ሙገር ካለ ግብ ተለያይተዋል፡፡

ሀዋሳ ላይ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አአ ከተማን ያስተናገደው ደቡብ ፖሊስ 4-0 አሸንፏል፡፡ የደቡብ ፖሊስን የድል ግቦች ወንድሜነህ አይናለም ፣ ሚካኤል ለማ ፣ ዘላለም እና ወንድይፍራው አስቆጥረዋል፡፡ ከመጥፎ አጀማመር በኀላ እያንሰራራ የሚገኘው ደቡብ ፖሊስ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ብቻ 12 ግቦች ተጋጣሚዎቹ ላይ አስቆጥሯል፡፡

PicsArt_1461684463726

ወደ አክሱም የተጓዘው ሙገር ሲሚንቶ ከአክሱም ከተማ ጋር ካለ ግብ ተለያይቷል፡፡

PicsArt_1461684562430

የተስተካካይ ጨዋታዎች ውጤቶች እና ቀጣይ ተስተካካይ ጨዋታዎች

አርብ ሚያዝያ 14 ቀን 2008

ነቀምት ከተማ 0-0 ነገሌቦረና (ነቀምት)

(የ8ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ)

 

13ኛ ሳምንት

ማክሰኞ ሚያዝያ 18 ቀን 2008

ደቡብ ፖሊስ 4-0 አአ ከተማ (ሀዋሳ)

አክሱም ከተማ 0-0 ሙገር ሲሚንቶ (አክሱም)

ረቡዕ ሚያዝያ 19 ቀን 2008

ነገሌ ቦረና ከ ጅማ አባ ቡና (ነገሌ ቦረና)

 

14ኛ ሳምንት

እሁድ ሚያዝያ 23 ቀን 2008

09:00 ሻሸመኔ ከተማ ከ አአ ከተማ (ሻሸመኔ)

09:00 ሙገር ሲሚንቶ ከ ባህርዳር ከተማ (መድን ሜዳ)

እሁድ ሚያዝያ 30 ቀን 2008

09:00 ጅማ አባ ቡና ከ አአ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)

 

15ኛ ሳምንት

ማክሰኞ ሚያዝያ 25 ቀን 2008

09:00 አርሲ ነገሌ ከ ጅማ አባ ቡና (አርሲ ነገሌ)

አርብ ሚያዝያ 28 ቀን 2008

09:00 አአ ከተማ ከ ነቀምት ከተማ (አበበ ቢቂላ)

09:00 ሰሜን ሸዋ ደብረብርሃን ከ ሙገር ሲሚንቶ (ደብረብርሃን)

picsart_1461655199502.jpg

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *