የአሰልጣኞች አስተያየት | ኢትዮ ኤሌክትሪክ 0-1 ቅዱስ ጊዮርጊስ

የአሰልጣኞች አስተያየት | ኢትዮ ኤሌክትሪክ 0-1 ቅዱስ ጊዮርጊስ

👉 “የዛሬው ጨዋታ ሽንፈት እኛን አይገልፀንም” – አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ

👉 “በእንቅስቃሴ ረገድ ብዙም ባያስደስትም ግን ማሸነፍ ችለናል” – አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ

ፈረሰኞቹ በአማኑኤል ኤርቦ ብቸኛ ግብ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1-0 በሆነ ውጤት አሸንፈው ሦስተኛ ተከታታይ ድላቸውን ካስመዘገቡበት ጨዋታ በኋላ የሁለቱም ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል።

አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ – ኢትዮ ኤሌክትሪክ

“የዛሬው ጨዋታ ሽንፈት እኛን አይገልፀንም። ከእስካሁኑ በተለየ ዛሬ የቀረብንበት አቀራረብ የተሻለ ነበር ነገር ግን ግብ አለመማስቆጠራችን እንድንሸነፍ አድርጎናል።”

አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ – ቅዱስ ጊዮርጊስ

“በእንቅስቃሴው ደስተኛ ባንሆንም የሚያስፈልገን ማሸነፉ ስለነበር እሱን አሳክተናል። ጫና እየበረታብን ሲመጣ መከላከሉን አጠናክረን ሶስት ነጥብ ይዘን ለመውጣት ሞክረናል።።”