”ትልቁ እና ወሳኙ ነገር ሻምፒዮን መሆናችን ነው” ሰርጆቪች ‘ሚቾ’ ሚሉቲን

ሰርቢያዊው የዩጋንዳ ብሄራዊ ቡድን ታክቲሺያን ሰርጆቪች ሚቾ ሚሉቲን ቡድናቸው የዴኤስቲቪ ሴካፋ ሲኒየር ቻሌንጅ ካፕ ዋንጫ ለ14ኛ ግዜ ካነሳ በኃላ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡ እኛም ለአንባቢያን በሚመች መልኩ አቅርበነዋል፡፡

ስለዩጋንዳ ክሬንስ የሴካፋ ቆይታ

”ወደ ኢትዮጵያ ይዘን የመጣነው በጣም ወጣት የሆነ ቡድን ነው፡፡ ከ19ኙ የቡድኑ ተጫዋቾችን ሶስቱ ብቻ ከ23 ዓመት በላይ ናቸው፡፡ 85 በመቶ የሚሆኑት ተጫዋቾች የሴካፋ ልምድ የሌላቸው ተጫዋቾች ነበሩ፡፡ ለኛ ጠቃሚ ልምድ የቀሰምንበት ውድድር ነበር፡፡
 
”የመጀመሪያ ጨዋታዎችን (ከኬንያ ጋር) ተሸንፈን ነበር የጀመርነው፡፡ ነገር ግን ስህቶቻችን አርመን ግብ ሳይቆጠርብን እስከፍፃሜ ድርስ ሄደናል፡፡ ጠንካራ ተከላካይ ክፍል እንዳለን አሳይተናል፡፡ ትልቁ እና ወሳኙ ነገር ሻምፒዮን መሆናችን ነው፡፡ አሁን ፊታችንን ወደቻን 2016 የምናዞር ይሆናል፡፡”

ስለተሰነዘረባቸው ትችት

”በሁሉም ውድድሮች ላይ የማሰለጥናቸው ብድኖች ለተሳታፊነት አይመጡም ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን እንጂ፡፡ በዩጋንዳ የሚገኙ አንዳንድ ሰዎች ይህ ቡድን ደካማ ነው ብለው ነበር፡፡ ሆኖም ግን እኛ ውድድሩን በማሸነፍ አፀፋውን መልሰናል፡፡ እኛ የተቹንን እናከብራለን፡፡ የምናከብረው ደግሞ ጨዋታዎችን በማሸፍ ነው፡፡”

ስለ ኤልያስ ማሞ ኤልያስ ማሞ

”የሴካፋ ዋንጫ ኮከብ ተጫዎች ተብሎ በመመረጡ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከለቀቅኩ በኃላ ኤልያስ በቂ የመጫወት ግዜ ባለማግኘቱ ትንሽ ዕድገቱ ተጓቶ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ጥሩ የሆኑ ፈጣሪ አማካዮች እያጣች ነው፡፡ ከዚህ በፊት ሙሉዓለም ረጋሳ እና አሸናፊ ግርማን የመሳሰሉ ፈጣሪ ተጫዋቾች ነበሩ፡፡ አሁን ግን በሚያሰጋ መልኩ ፈጣሪ ተጫዋቾችን እያጣች ነው፡፡ ኤልያስ በቀጣዩ ግዜ የተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚደርስ ተስፋ አለኝ፡፡”

ስለክሬንስ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ምድብ

”የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ምድባችንን እየመራን ነው፡፡ በ2015 ኤኳቶልያል ጊኒ ባዘጋጀችው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ከጫፍ ደርሰን ነበር የቀረነው፡፡ አሁን እራሳችንን በደንብ እየመረመርን ነው፡፡ አሁንም ስራዎችን መስራት አለብን፡፡”

 ስለኢትዮጵያ የሴካፋ መስተንግዶ

”ኢትዮጵያ ውድድሩን በማዘጋጀቷ ደስተኛ ነው፡፡ ሴካፋ በ2014 አልተካሄደም ነበር አሁን ግን ኢትዮጵያ የአዘጋጅነቱን ሀላፊነት ተቀብላ ጥሩ የሆነ ውድድር ማዘጋጀት ችላለች፡፡ ይህም ኢትየጵያ በ2020 የቻን አዘጋጅ መሆን መቻሏ ተገቢ መሆኑን አይቻለው፡፡ እንደኳፍ መስራች አባልነታችሁ ካፍ በ2025 የአፍሪካ ዋንጫን ማዘጋጀት ዕድል ለኢትዮጵያ መስጠት አለበት ብዬ አስባለው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ለነበረን ጥሩ ቆይታ ኔክሰስ ሆቴል እና ኬሮደን ሆቴልን ማመስገን እፈልጋለው፡፡ ”

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *