ፐሪሚየር ሊግ ፡ ድቻ ከ መከላከያ ነጥብ ሲጋሩ ቴዎድሮስ በቀለ የወላይታ ድቻን መረብ ከ9 ጨዋታዎች በኋላ ደፍሯል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ሲጀምር ቦዲቲ ላይ ወላይታ ድቻ ከ መከላከያ ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል፡፡ ቴዎድሮስ በቀለም ወንድወሰን አሸናፊ እና ወላይታ ድቻ ላይ በሁለተኛው ዙር ለመጀመርያ ጊዜ ግብ ያስቆጠረ ተጫዋች ሆኗል፡፡

በድንቅ የደጋፊዎች ድባብ እና ፈጣን እንቅስቃሴ በታጀበው ጨዋታ የግብ ቅድሚያውን የወሰዱት ወላይታ ድቻዎች ነበሩ፡፡ በ18ኛው ደቂቃ በድሉ መርዕድ ከቅታት ምት ያሻማውን ኳስ ቴዎድሮስ በቀለ በእጁ በመንካቱ የተሰጠውን የፍፁም ቅጣት ምት አምበሉ አላዛር ፋሲካ ወደ ግብነት ቀይሯታል፡፡

PicsArt_1465832177166

መከላከያዎች ከግቡ መቆጠር በኋላ የአቻነት ግብ ለማግኘት ጫና ፈጥረው የተንቀሳቀሱ ሲሆን በ38ኛው ደቂቃ ለድቻ ግብ መቆጠር አስተዋፅኦ ያደረገው ቴዎድሮስ በቀለ ከማዕዘን የተሸገረውን ኳስ በግንባሩ በመግጨትመከላከያን አቻ አድርጓል፡፡ ይህች ግብ በሁለተኛው ዙር በወላይታ ድቻ ላይ የተቆጠረች የመጀመርያ ግብ ሆና ተመዝግባለች፡፡

PicsArt_1465832277918

የድቻው ግብ ጠባቂ ወንድወሰን አሸናፊ ከ930 ደቂቃዎች በላይ መረቡን ባለማስደፈር በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ታሪክ በርካታ ደቂቃ ግብ ያልተቆጠረበት ኢትዮጵያዊ ግብ ጠባቂ ለመሆን ችሏል፡፡ (የሊጉ ሪኮርድ የተያዘው በቅዱስ ጊዮርጊሱ ዩጋንዳዊ ግብ ጠባቂ ሮበርት ኦዶንካራ ነው፡፡)

PicsArt_1465832080944የድቻ ደጋፊዎች ቡድናቸውን በዚህ መልኩ ሲያበረታቱ ነበር

የደረጃ ሰንጠረዥ

PicsArt_1465833112253

ቀሪ የ23ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ፕሮግራም
ማክሰኞ ሰኔ 7 ቀን 2008

09፡00 ሀዲያ ሆሳዕና ከ አዳማ ከተማ (ሀዋሳ)

11፡30 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ (አአ ስታድየም)

ረቡዕ ሰኔ 8 ቀን 2008

09፡00 ድሬዳዋ ከተማ ከ ኤሌክትሪክ (ድሬዳዋ)

09፡00 ሲዳማ ቡና ከ ኢትዮጵያ ቡና (ይርጋለም)

09፡00 ዳሽን ቢራ ከ አርባምንጭ ከተማ (አዳማ አበበ ቢቂላ)

09፡00 ሀዋሳ ከተማ ከ ደደቢት (ሀዋሳ)


 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *