የፕሪሚየር ሊጉ ሁለተኛ ዙር መጋቢት 5 ይጀመራል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2ኛ ዙር በመጪው መጋቢት 5 እንደሚጀመር የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡ በመጋቢት ወር በሚካሄደው የአፍሪካ ወጣቶች አትሌቲክስ ቻምፒዮና ምክንያት ውድድሩ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የሊጉ የአዲስ አበባ ጨዋታዎች በአበበ ቢቂላ ስታድየም የሚደረጉ ይሆናል፡፡

የሁለተኛ ዙር ጨዋታዎቹ እስከ ነሃሴ 7 ድረስ የሚደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታዎችን የሚጀምረው በሰኔ ወር በመሆኑ ፌዴሬሽኑ የሊጉ ጨዋታዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እንዳቀደ ተነግሯል፡፡

የ2ኛው ዙር ጨዋታዎች የሚካሄዱባቸው ሳምንታት የሚከተሉት ናቸው፡-

14ኛ ሳምንት – መጋቢት 5 እና 6

15ኛ ሳምንት – መጋቢት 12 እና 13

16ኛ ሳምንት – መጋቢት 19 እና 20

17ኛ ሳምንት – መጋቢት 26 እና 27

18ኛ ሳምንት – ሚያዝያ 3 እና 4

19ኛ ሳምንት – ሚያዝያ 10 እና 11

20ኛ ሳምንት – ሚያዝያ 17 እና 18

21ኛ ሳምንት – ሚያዝያ 25 እና 26

22ኛ ሳምንት – ግንቦት 1 እና 2

23ኛ ሳምንት – ግንቦት 8 እና 9

24ኛ ሳምንት – ግንቦት 22 እና 23

25ኛ ሳምንት – ግንቦት 29 እና 30

26ኛ ሳምንት – ሰኔ 6 እና 7

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *