ኮንፌድሬሽን ካፕ፡ ደደቢት ዋሪ ዎልቭስን ባህርዳር ላይ ያስተናግዳል

በአፍሪካ ኮንፌድሬሽን ካፕ አንደኛ ዙር የመልስ ጨዋታ ደደቢት ነገ ዋሪ ዎልቭስን በባህርዳር ስታድየም ያስተናግዳል፡፡

በመጀመርያው ጨዋታ 2-0 ተሸንፎ የተመለሰው ደደቢት ውጤቱን ቀልብሶ ወደ ተከታዩ ዙር ለማለፍ ፈተና ይገጠመዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በጨዋታው በደደቢት በኩል ጋናዊው ግብ ጠባቂ ሱሌማና አቡበከር እና ያሬድ ዝናቡ በጨዋታው የማይሰለፉ ሲሆን ከኮት ዲ ኦር ጋር በተደረገው ጨዋታ በጉዳት ከሜዳ የወጣው ሳምሶን ጥላሁን ከጉዳቱ አገግሞ ይሰለፋል ተብሏል፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *