ማላዊ የኢትዮጵያ ምድብ ውስጥ መግባቷን አረጋገጠች

ለ2015 የሞሮኮ አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ምድብ ውስጥ ለመግባት በተደረገ የቅድመ ማጣርያ ጨዋታ ማላዊ ቤኒንን አሸንፋ የነ ኢትዮጵያን ምድብ መቀላቀሏን አረጋግጣለች፡፡

በኮቶኑ በተካሄደው የመጀመርያ የማጣርያ ጨዋታ 1-0 ተሸንፋ የተመለሰችው ማላዊ በሜዳዋ ባደረገችው የመልስ ጨዋታ ሙሉውን 90 ደቂቃ 1-0 በሆነ ውጤት ያጠናቀቁ ሲሆን አሸናፊዎቹን ለመለየት በተሰጠው የመለያ ምት ማላዊ 4-3 አሸንፋ ወደ ምድብ ማጣርያው መቀላቀሏን አረጋግጣለች፡፡

የምድብ ማጣርያ ውድድሮች በነሀሴ ወር መጨረሻ ሲጀምሩ ኢትዮጵያ ከአልጄርያ ፣ ማሊ ከ ማላዊ የመጀመርያ ጨዋቸውን ያደርጋሉ፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *