ጥላሁን ወልዴ ለኢትዮጵያ ቡና ፈረመ

የመከላከያው የመስመር አማካይ ጥላሁን ወልዴ ለኢትዮጵያ ቡና መፈረሙን ክለቡ አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያ ቡና በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ዛሬ እንዳስታወቀው ጥላሁን ለ2 አመታት ለአደገኞቹ ለመጫወት ፊርማውን አኑሯል፡፡

በመስመር ተከላካይነት ፣ አማካይነት እና መሃል አማካይነት መጫወት የሚችለው ጥላሁን ቡናን ለቆ የሄደው ኤፍሬም አሻሞን ቦታ ይሸፍናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ጥላሁን በኒያላ ፣ በአየር ኃይል ፣ ሙገር እና መከላከያ የተጫወተ ሲሆን ለብሄራዊ ቡድኑም በ2012 የሴካፋ ውድድር ላይ ተጫውቷል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *