ፕሪሚየር ሊግ ፡ ወልድያ ከፕሪሚየር ሊግ መውረዱን አረጋገጠ

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወልድያ ከፕሪሚየር ሊጉ መውረዱን ሲያረጋግጥ ሙገር ሲሚንቶም የወልድያን እግር ሊከተል ተቃርቧል፡፡

መልካ ቆሌ ላይ አርባምንጭ ከነማን ያስተናገደው ወልድያ 1-0 ተሸንፏል፡፡ ሽንፈቱን ተከትሎም 3 ጨዋታ እየቀረው 12ኛ ደረጃ ላይ ካለው ኤሌክትሪክ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት 12 በመድረሱ ባለፈው አመት ወደነበረበት ብሄራዊ ሊግ መውረዱን አረጋግጧል፡፡

አሰላ ላይ አዳማ ከነማን ያስተናገደው ሙገር ሲሚንቶ 1-1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቶ ከኤሌክትሪክ ጋር የነበረውን ልዩነት የማጥበብ እድሉን አበላሽቷል፡፡ ሙገር 12ኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው ኤሌክትሪክ ጋር ያለው የነጥ ልዩነት 4 ሆኗል፡፡

ይርጋለም ላይ መከላከያን ያስተናገደው ሲዳማ ቡና 0-0 አቻ ተለያይቶ ለዋንጫ የነበረው ተስፋ አክትሟል፡፡ ሲዳማ ቡና የሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ሶስቱንም ጨዋታ አሸንፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሶስቱንም ጨዋታ መሸነፍ ይኖርበታል፡፡

አዲስ አበባ ስታድየም ላይ ወላይታ ድቻን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ቡና 0-0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል፡፡ ኢትዮጵያ ቡና በአንዋር ያሲን እየተመራ የመጀመርያ ነጥቡን ሲያገኝ ከ5 ተከታታይ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ ያገኘው የመጀመርያ ነጥብ ሆኗል፡፡

የ23ኛ ሳምንት ውጤቶች የሚከተሉት ናቸው

ኤሌክትሪክ 0-4 ደደቢት

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1-1 ሀዋሳ ከነማ

ዳሽን ቢራ 1-2 ቅዱስ ጊዮርጊስ

ሲዳ ቡና 0-0 መከላከያ

ሙገር ሲሚንቶ 1-1 አዳማ ከነማ

ወልድያ 0-1 አርባምንጭ ከነማ

ኢትዮጵያ ቡና 0-0 ወላይታ ድቻ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *