ኢትዮጵያ ቡና ካልተለመደ ምንጭ አንድ ተጫዋች አስፈርሟል

በክልል ክለቦች ዓመታዊ ውድድር ላይ ጥሩ ጊዜ ያሳለፈው ተጫዋች ማረፊያው ኢትዮጵያ ቡና ሆኗል።

በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ወደ ቡድኑ እየቀላቀለ የሚገኘው ኢትዮጵያ ቡና በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ላይ የውድድሩ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ የሆነውን አጥቂ አንተነህ ተፈራን ከሻኪሶ ከተማ አስፈርሟል።

አብዛኛውን ውድድር በሜዳ ተገኝተው የተከታተሉት አሰልጣኝ ተመስገን ዳና የዚህ ወጣት ተጫዋች እንቅስቃሴ እንደማረካቸው እና ተጫዋቹን ለማስፈረም እንዲወስኑ እንዳደረጋቸው አውቀናል። አንተነህ ለምን ያህል ዓመት እንደፈረመ ግን የተገለፀ ነገር የለም።

ፎቶ ምንጭ – ዳጉ ስፖርት