ዋልያዎቹ ጨዋታውን በሚያደርጉበት ስታድየም ልምምድ ሰርተዋል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አልጄርያ ከከተመ 3ኛ ቀኑን ይዟል፡፡ በዛሬው እለትም ጨዋታው በሚደረግበት ሙስታፋ ቻክር ስታድየም ልምምዱን አድርጓል፡፡

በሃገሪቱ ባለው ቅዝቃዜ የተቸገሩት ዋልያዎቹ ከጨዋታው በፊት ባደረጉት የመጨረሻ ልምምዳቸው ቀለል ያሉ ልምምዶችን የሰሩ ሲሆን ቋሚ አሰላለፉን በሚያሳይ መልኩ ለሁለት በመከፈል ተጫውተዋል፡፡ የቆሙ ኳሶች አጠቃቀም ላይም ልምምድ ሰርተዋል፡፡

PicsArt_1458846932942

የብሄራዊ ቡድኑ ረዳት አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ወላጅ አባቱ ከዚህ አለም በሞት በመለየታቸው ምክንያት የብሄራዊ ቡድኑን ተለይቶ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል፡፡

የአልጄርያ እና ኢትዮጵያ ጨዋታ በቀዝቃዛማዋ ብሊዳ ከተማ በሚገኘው ሙስጣፋ ሻክር ስታድየም ነገ ምሽት 04:30 ላይ ይካሄዳል፡፡

PicsArt_1458847177988

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *