ሰጎኖቹ የመስመር አጥቂውን የግላቸው አድርገዋል

ሰጎኖቹ የመስመር አጥቂውን የግላቸው አድርገዋል

ከወልዋሎ ጋር ጥሩ ጊዜ ያሳለፈው የመስመር አጥቂ ማረፊያው ነገሌ አርሲ ሆኗል።

የሊጉ ክስተት የነበሩት ነገሌ አርሲዎች በዝውውሩ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ጠንካራ ዝውውሮች እየፈፀሙ ይገኛሉ። ከሰዓታት በፊት ከዐፄዎቹ ጋር ድንቅ የውድድር ዓመት ያሳለፈውን በረከት ግዛውን የግላቸው ሲያደርጉ አሁን ደግሞ እንዳልካቸው ጥበቡን ለማስፈረም ተስማማተዋል።

በአርባምንጭ ከተማ የእግርኳስ ጅማሮን ያደረገው ባለ ግራ እግሩ የመስመር አጥቂ በኦሜድላ እና በዘንድሮ ዓመት በወልዋሎ ከኢትዮጵያ ዋንጫ ድል ጋር የተሳካ ዓመት አሳልፏል። አሁን መዳረሻው ነገሌ አርሲ ሊሆን ለሁለት ዓመት ተስማምቷል።