ፕሪሚየር ሊግ ፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመሪው ያለውን የነጥብ ልዩነት አጠበበ

በኢትዮጵያ ፐሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት ዛሬ በተካሄዱ 5 ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ አሸንፎ ከመሪው ጋር ያለውን ርቀት ሲያጠብ ዳሽን እና ሙገር ሲሚንቶም በሜዳዳው ድል ቀንቷቸዋል፡፡

8 ሰአት አበበ ቢቂላ ላይ ወላይታ ድቻን ያስተናገደው ኤሌክትሪክ 1-1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል፡፡ ወላይታ ድቻ አዲሱ ተስፋዬ በግንባሩ ገጭቶ ባስቆጠረው ግብ 1-0 ቢመራም ኤሌክትሪክ ዊልያም ኤሳድጆ ባስቆጠረው ግሩም የቮሊ ግብ አቻ ለመሆን በቅቷል፡፡

በ9 አሰት ጎንደር ላይ በተደረገው የዳሽን ቢራ እና ሀዋሳ ከነማ ጨዋታ ዳሽን በራ 2-1 አሸንፏል፡፡ ሀዋሳ ከነማ ተመስገን ተክሌ በ44ናው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ 1-0 ሲመራ ቢቆይም ሚካኤል ጆርጅ በ45ኛው እና አሌክስ በ90ኛው ደቂቃ ባስቆጠሩት ግብ ዳሽን በራ ጨዋታውን 2-1 አሸንፎ ወጥቷል፡፡

በተመሳሳይ ሰአት አሰላ ላይ መከላከያን ያስተናገደው ሙገር ሲሚንቶ በሄኖክ ፍስሃ ግብ 1-0 ሲያሸንፍ አርባምንጭ ላይ አርባምንጭ ከነማ ከ አዳማ ከነማ ካለግብ 0-0 ተለያይተዋል፡፡

አበበ ቢቂላ ላይ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶት በነበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ደደቢት ጨዋታ ፈረሰኞቹ በቀላሉ 2-0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል፡፡ የቅዱስ ጊዮዮጊስን ቀዳሚ ግብ ተከላካዩ ሳላዲን ባርጊቾ በግሩም ሁኔኔ ሲያስቆጥር አሉላ ግርማ በሁለተኛው አጋማሽ ተጨማሪዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡

ትላንት በተደረጉ ጨዋታዎች ኢትዮጵያa ቡና ወልድያን 5-2 ሲያሸንፍ ንግድ ባንክ ከ ሲዳማ ቡና 1-1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

ሊጉ በመጪው እሁድe በተስተካካይ ጨዋታዎች ሲቀጥል ቦዲቲ ላይ ወላይታ ድቻ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ ሀዋሳ ላይ ሀዋሳ ከነማ ከ ደደቢት ፤ አበበ ቢቂላ ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከ ኤሌክትሪክ ተጫውተው 1ኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ይዘጋል፡፡

ሊጉን ሲዳማ ቡና በ27 ነጥቦች ሲመራ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ24 ይከተላል፡፡ የከፍተኛ ግብ አግቢነቱን ቢንያም አሰፋ በ11 ግብ ይመራል፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *