የኢትዮጵያ ጥሎማለፍ የ2009 የውድድር ዘመን ድልድል ማክሰኞ በሶዶ ከተማ መውጣቱ የሚታወስ ነው፡፡ 5 የከፍተኛ ሊግ እና 16 የፕሪምየር ሊግ ክለቦችን ያካተተው ውድድር ቅዳሜ እና እሁድ በሚደረጉ የ1ኛ ዙር ጨዋታዎች እንዲጀመር ፕሮግራም ቢወጣም 4 የከፍተኛ ሊግ ክለቦች በተለያዩ ምክንያቶች መወዳደር እንደማይችሉ በመግለጻቸው በአንደኛው ዙር የሚደረገው ጨዋታ አንድ ብቻ ሆኗል፡፡
ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት ፣ ድሬዳዋ ፖሊስ ፣ ፌዴራል ፖሊስ እና አራዳ ክፍለከተማ እንደማይሳተፉ ያሳወቁ ክለቦች ሲሆኑ ሽረ እንደዳስላሴ ብቻ በውድድሩ ላይ እንደሚሳተፍ ታውቋል፡፡
በዚህም መሰረት ፋሲል ከተማ ፣ ወልድያ ፣ አዲስ አበባ ከተማ እና ጅማ አባ ቡና በፎርፌ ወደ ቀጣዩ ዙር ሲያልፉ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሽረ እንዳስላሴ ቅዳሜ 11:30 ላይ በአዲስ አበባ ስታድየም በሚያደርጉት ጨዋታ ወደ ቀጣዩ ዙር የሚገባው ቡድን ይለያል፡፡
1ኛ ዙር
ቅዳሜ የካቲት 11 ቀን 2009
11:30 ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከ ሽረ እንዳስላሴ (አአ ስታድየም)
የ2ኛ ዙር ተጋጣሚዎች
(ቀን እና ሰአት ወደፊት ይገለጻል)
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ድሬዳዋ ከተማ
መከላከያ ከ ሀዋሳ ከተማ
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ወልድያ
ፋሲል ከተማ ከ አዳማ ከተማ
ደደቢት ከ ጅማ አባ ቡና
አአ ከተማ ከ ሲዳማ ቡና
ወላይታ ድቻ ከ አርባምንጭ ከተማ
የሽረ እንዳስላሴ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ አሸናፊ ከ ኢትዮጵያ ቡና