አል አህሊ ከ ጅማ አባ ጅፋር – ቀጥታ ስርጭት

ዓርብ ታኅሳስ 5 ቀን 2011
FT አል አህሊ🇪🇬 2-0 🇪🇹ጅማ አባ ጅፋር
7′ ናስር ማሀር
38′ ማርዋን ሞሀሰን

90+4′ ቅያሪ (ጅማ አባ ጅፋር) ፡ አስቻለው ግርማ ወጥቶ ኤርሚያስ ኃይሉ ገብቷል፡፡

90+3′ ከሪም ኔድቬድ ከን መስመር ያሻገረውን ኳስ ከግቡ አጠገብ የነበረው ሚዶ ጋብር ሳይደርስበት ቀርቷል፡፡ ሌላ ጎል ለመሆን የተቃረበ ኳስ …

90′ ማርዋን አሽራፍ ያሻገረውን ኳስ ሞሀሰን በግንባሩ ገጭቶ ሲያመቻችለት ሚዶ ጋብር ከቀኝ የሳጥኑ ክፍል በግራ እግሩ የሞከረውን ኳስ ዳንኤል አጄይ አድኖበታል፡፡

84′ ሞሀሰን ያመቻቸለትን ግልጽ ኳስ ተቀይሮ የገባው ዋሊድ ሶሊን ወደ ውጪ ሰዶታል፡፡

83′ ማርዋን ሞሀሰን በሁለት የጅማ ተከላካዮች መሐል የተቐበለውን ኳስ ወደፊት ገፍቶ የሞከረው ኳስሷሚውን ገጭቶ ወደ ውጪ ወጥቷል፡፡

82′ ጅማ አባ ጅፋሮች ኳስ መቆጣጠር ቢችሉም ወደ ማጥቃት ወረዳው የደረሱት በጥቂት አጋጣሚዎች ነው፡፡ የግብ እድሎች እየፈጠሩ የሚገኙትም ከርቀት በሚመቱ ኳሶች ነው፡፡

80′ ቅያሪ (አል አህሊ) ፡ መሐመድ ሸሪፍ ወጥቶ በካፍ የዓመቱ ኮቦች ሽልማት የመጨረሻ 10 ውስጥ የተካተተው ዋሊድ ሶሊማን ገብቷል፡፡

78′ ቅያሪ (ጅማ አባ ጅፋር) ፡ መስዑድ መሐመድ ወጥቶ በቅድመ ማጣርያው ሶስት ጎሎች ያስቆጠረው ማማዱ ሲዴቢ ገብቷል፡፡

75′ ጅማ አባ ጅፋር ያለፉትን አስር ደቂቃዎች ኳስ በመቆጣጠር ረገድ የተሻለ እየተንቀሰቀሰ ይገኛል፡፡

73′ ኄኖክ ገምቴሳ ከሳጥኑ አቅራቢያ የተገኘውን የቅጣት ምት በቀጥታ ሞክሮ በግቡ አናት ወደ ውጪ ወጥቷል፡፡

68′ ቅያሪ (አል አህሊ) ፡ መሀመድ ሀሞውዲ ወጥቶ ሚዶ ጋብር ገብቷል፡፡

64′ ቅያሪ (አል አህሊ) ፡ ሆሳም አሻወር ወጥቶ ሔሻም መሐመድ ገብቷል፡፡፡፡

60′ በመጀመርያው አጋማሽ ወደ ቀኝ አጋድሎ የነበረው የአል አህሊ የማጥቂያ መስመር በዚህ አጋማሽ ወደ ግራ አዘንብሏል፡፡ የግራ መስመር ተከላካዩ አይማን አሽረፍ የማጥቃት እንቅስቃሴም አስፈሪ ነው፡፡

55′ አይመን አሽረፍ በድጋሚ ተመሳሳይ ከሆነ ቦታ እና በተመሳሳይ አካሄድ ያሻገረውን ኳስ አሁንም ማርዋን ሞሀሰን በግምባሩ ገጭቶ ዳንኤል አጄይ መልሶበታል፡፡ የጅማ የተከላካይ መስመር ደቂቃዎች እየገፉ በሔዱ ቁጥር ይበልጥ ለስህተት እና ለጥቃት የተጋለጠ ሆኗል፡፡

53′ አይመን አሽረፍ በጥሩ ሁኔታ ከግራ መስመር ያሻገረውን ኳስ ነጻ አቋቋም ላይ የነበረው ማርዋን ሞሀሰን ሞክሮ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል፡፡

48′ ከመስመር የተሸገረውን ኳስ መሐመድ ሸሪፍ ከዳንኤል አጄይ ቀድሞ በግንባሩ ቢገጭም ወደ ውጪ ወጥበታል፡፡ የአባ ጅፋር የመከላከል አደረጃጀት በዚህም አጋማሽ በቀላሉ ለጥቃት የተጋለጠ ሆኗል፡፡

02:05 ሁለተኛው አጋማሽ ተጀምሯል፡፡


እረፍት

የመጀመርያው አጋማሽ በአል አህሊ 2-0 መሪነት ተጠናቋል፡፡

43′ አስቻለው ግርማ ከርቀት የተሸገረለትን ኳስ ከህሊ ተከላከዮች አምልጦ ቢመታውም በግቡ አናት ወደ ውጪ ወጥቷል፡፡

38′ ማርዋን ሞሀሰን በጅማ አባ ጅፋር ተከላካዮች መሐል ሆኖ ከአህመድ ሀሞውዲ የተቀበለውን ኳስ በጥሩ ሁኔታ በመዞር ራሱን ነጻ ካደረገ በኋላ በዳንኤል አጄይ መረብ ላይ አሳርፎታል፡፡ 2-0

34′ አህመድ ሀሞውዲ በፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውስጥ በድጋሚ ያገኘውን መልካም አጋጣሚ ሞክሮ በግቡ አናት ወደ ውጪ ወጥቶበታል፡፡

30′ የአል አህሊው የቀኝ መስመር ተከላካይ ከሪም ኔድቬድ የሚያደርገው የፊት ለፊት ሩጫ ለጅማ አባ ጅፋር ተከላካዮች ፈታኝ ሆኗል፡፡

29′ ጅማ አባ ጅፋሮች በአጫጭር ቅብብሎች ወደ ግብ በተደጋጋሚ ለመድረስ የሚያደርጉት ጥረት በአል አህሊዎች በቀላሉ እየከሸፈ ይገኛል፡፡

25′ አህመድ ሀሞውዲ ከኔድቬድ የተሸገረለትን ኳስ ሞክሮ የግቡ አግዳሚ መልሶበታል፡፡ለግብ እጅግ የቀረበ ነበር፡፡

22′ አህመድ ሀሞውዲ ከግማሽ ጨረቃው አካባቢ የመታው ኳስ ኢላማውን ስቶ በግቡ አናት ወደ ውጪ ወጥቷል፡፡

15′ አል አህሊ በቀኝ መስመር ላይ አተኩሮ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡

10′ መስዑድ መሐመድ በሳጥኑ የቀኝ ክፍል የመታውን ኳስ ግብ ጠባቂው በቀላሉ ይዞበታል፡፡

ጎል

7′ ከሪም ኔድቪድ የመታው ኳስ የግቡን ቋሚ ለትሞ ሲመለስ በጥሩ አቋቋም ላይ የነበረው ናስር ማሀር አል አህሊን ቀዳሚ ያደረገች ጎል አስቆጥሯል፡፡

3′ ከመስመር የተሸገረውን ኳስ ሞሀስን ሳይደርስበት ቀርቷል፡፡ የመጀመርያ የአል አህሊ የግብ አጋጣሚ…

1፡00 ጨዋታው ተጀመረ

12:50 ሁለቱ ቡድኖች በማሟሟቅ ላይ ይገኛሉ::

አሰላለፍ
አል አህሊ ጅማ አባ ጅፋር
ሸሪፍ ኢክራሚ
ከሪም ናድቬድ
ሳሊፍ ኩሊባሊ
መሐመድ ሀኒ
አይማን አሽረፍ
ሆሳም አሻወር
አመር ኤል ሱሊያ
መሐመድ ሸሪፍ
ናስር ማሀር
አህመድ ሀሞውዲ
ማርዋን ሞህሰን
29 ዳንኤል አጄይ
2 ዐወት ገብረሚካኤል
4 ከድር ኸይረዲን
22 አዳማ ሲሶኮ (አ)
14 ኤልያስ አታሮ
6 ይሁን እንደሻው
3 መስዑድ መሐመድ
26 ኄኖክ ገምቴሳ
17 አስቻለው ግርማ
20 ቢስማርክ አፒያ
12 ዲዲዬ ለብሪ
ተጠባባቂዎች ተጠባባቂዎች
ዓሊ ሎትፊ
ሔሻም መሐመድ
ሚዶ ጃባር
ኢስላም ሞሀርብ
ዋሊድ ሶሊማን

1 ዘሪሁን ታደለ
5 ተስፍዬ መላኩ
15 ያሬድ ዘውድነህ
19 አክሊሉ ዋለልኝ
10 ኤልያስ ማሞ
9 ኤርሚያስ ኃይሉ
7 ሲዲቤ ማማዱ
ዳኞች
ዋና ዳኛ – ሳዶክ ሴልሚ (ቱኒዚያ)
1ኛ ረዳት – አይመን ኢስማኤል (ቱኒዚያ)
2ኛ ረዳት –  አቲያ አምሳድ (ሊቢያ)
ውድድር | ቻምፒየንስ ሊግ አንደኛ ዙር
ቦታ| አሌክሳንድሪያ
ሰዓት | 1:00