በመጪው መስከረም ወር ኮንጎ ብራዛቪል ለምታዘጋጀው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ለማለፍ ከካሜሮን አቻው ጋር ተደልድሎ ነበረው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን በድምር ውጤት 4ለ2 ተሸንፎ ከውድድሩ ውጪ ሆኗል፡፡ ቅዳሜ ዕለት ያውንዴ ላይ በተደረገው የመልስ ጨዋታ ሉሲዎች 2ለ1 ተሸንፈዋል፡፡ ሽታዬ ሲሳይ በ1ኛው ደቂቃ ኢትዮጵያን መሪ የምታደርግ ግብ ማስቆጠር ብትችልም ብሄራዊ ብድኑ በተቆጠሩበት 2 ግቦች 2ለ1 ተሸንፎ ከውድድሩ ውጪ ሆኗል፡: