በካሜሩን አስተናጋጅነት ለሚስተናገደው የ2016 የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ማጣርያ የመልስ ጨዋታ ለማድረግ የአልጄርያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ትላንት ሌሊት 07:00 ላይ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡
30 የልኡካን ቡድን በመያዝ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት አልጄርያውያን በሴቶች ብሄራዊ ቡድን የቡድን መሪ ቾል ቤል መሪነት አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡
ቡድኑ ዛሬ 10:00 ላይ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ማህበር ሜዳ ላይ የመጀመርያ ልምምዱን ሰርቷል፡፡ በነገው እለትም በተመሳሳይ ሰአት በአዲስ አበባ ስታድየም ልምምድ ያደርጋሉ፡፡
የአልጄርያ ብሄራዊ ቡድን የመጀመርያውን ጨዋታ በዴልያ ሮዜኪ የ68ኛ ደቂቃ ጎል 1-0 ማሸነፉ የሚታወስ ነው፡፡
በተያያዘ ዜና ቅዳሜ የሚደረገውን የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የሚመሩት ዳኞች ከደቂቃዎች በፊት አዲስ አበባ መግባታቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡