የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ብሄራዊ ቡድኑ ከማሊ ጋር ለሚያደርገው 3ኛ የምድብ ማጣርያ ጨዋታ 28 ተጫዋቾችን ይፋ አድርጓል፡፡
በምርጫው አሰልጣኝ ማርያኖ ባሬቶ በመጀመርያ ሁለት ማጣርያዎች የተጠቀሙባቸው አብዛኛዎቹን ተጫዋቾች ያካተቱ ሲሆን አዳዲስ ተጫዋቾችነም ጥሪ ደርሷቸዋል፡፡
ባለፈው የውድድር ዘመን በፕሪሚየር ሊጉ ድንቅ አቋም ያሳዩት አንተነህ ተስፋዬ እና ፍሬው ሰለሞን ለመጀመርያ ጊዜ የብሄራዊ ቡድኑ ጥሪ ሲደርሳቸው አሚን አስካር እና ዋሊድ አታም በስብስቡ ተካተዋል፡፡
የተጫዋቾቹ ዝርዝር ይህንን ይመስላል፡፡
ግብ ጠባቂዎች
ጀማል ጣሰው – መከላከያ
ሲሳይ ባንጫ – ደደቢት
ታሪክ ጌትነት – ደደቢት
ተከላካዮች
ቶክ ጄምስ – ኢትዮጵያ ቡና
አበባው ቡታቆ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
ብርሃኑ ቦጋለ – ደደቢት
አክሊሉ አየነው – ደደቢት
ሳላዲን በርጊቾ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
አሉላ ግርማ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
አንዳርጋቸው ይላቅ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
ዋሊድ አታ – ቢኬ ሃከን (ስዊድን)
አንተነህ ተስፋዬ – አርባምንጭ ከነማ
አማካዮች
ሽመልስ በቀለ – ፕትሮጄት (ግብፅ)
ታደለ መንገሻ – ደደቢት
ምንተስኖት አዳነ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
አስራት መገርሳ – ዳሽን ቢራ
አዳነ ግርማ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
ዩሱፍ ሳላህ – ፍሪ ኤጀንት
ኤፍሬም አሻሞ – ኢትዮጰያ ንግድ ባንክ
ናትናኤል ዘለቀ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
ምንያህል ተሾመ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
ፍሬው ሰለሞን – መከላከያ
ዳዊት እስጢፋኖስ – ኢትዮጵያ ቡና
አሚን አስካር – ብራን (ኖርዌይ)
አጥቂዎች
ጌታነህ ከበደ – ቢድቬትስ ዊትስ (ደ/አፍሪካ)
ሳላዲን ሰኢድ – አል አህሊ (ግብፅ)
ኡመድ ኡክሪ – አልኢትሃድ አሌሳንድሪያ (ግብፅ)
ዳዋ ኢቲሳ – ናሽናል ሴሚንቶ
ብሄራዊ ቡድኑ ከማሊ ጋር በአዲስ አበባ እና ባማኮ ላይ በ5 ቀናት ውስጥ (ኦክቶበር 11 እና 15) ጨዋታ የሚያደርግ ሲሆን አሰልጣኝ ማርያኖ ባሬቶ ሴፕቴምበር 23/2014 ዝግጅት እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል፡፡