ፌዴሬሽኑ የዋና ፀኃፊው የሥራ መልቀቁያ መቀበሉን አስታወቀ

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ኢያሱ መርሐ ፅድቅ ያቀረቡትን የሥራ መልቀቂያ መቀበሉን አስታውቋል።

ባለፈው ዓመት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ፀኃፊ ሆነው የተሾሙት ኢያሱ መርሐ ፅድቅ (ዶ/ር) ከሥራቸው ለመልቀቅ ጥያቄ ማቅረባቸውን የገለፀው ፌዴሬሽኑ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ ከትናንት የካቲት 4 ቀን 2012 ጀምሮ ከፌዴሬሽኑ ጋር መለያየታቸውን በድረ-ገፁ አስታውቋል።

እንደ ፌዴሬሽኑ ገለፃ ግለሰቡን በመተካት የህዝበረ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ባህሩ ጥላሁን በጊዜያዊነት ቦታውን የሚሸፍኑ ይሆናል።

የፌዴሬሽኑ ዋና ፀኃፊነት ቦታ ባለፉት ዓመታት መረጋጋት ከማይታይባቸው ቦታዎች አንዱ ሲሆን ባለፉት 5 ዓመታት አምስት ግለሰቦች በቋሚ እና በጊዜያዊነት ሰርተዋል።

© ሶከር ኢትዮጵያ